Daily Archives: March 18, 2012

ሰበር ዜና – የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዙሪያ የተነሣው የእሳት ቃጠሎ በቁጥጥር ሥር ዋለ

መጋቢት 8/2004 ዓ.ም፤ ማርች 17/2012/  በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊበን ዝቋላ ወረዳ አዱላላ ከተማ የሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በሚገኝበት ተራራ በስተምሥራቅ አቅጣጫ ዛሬ፣ መጋቢት 8 ቀን 2004ዓ.ም ቀትር ላይ የተነሣው የእሳት ቃጠሎ ማምሻውን በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተሰማ፡፡ በቃጠሎው ሁለት ጋሻ መሬት የሚሸፍን ደን መውደሙ ተነግሯል፡፡

የገዳሙ መነኰሳት ከስፍራው በስልክ እንደገለጹት÷ ዛሬ ቀትር ላይ በገዳሙ ዙሪያ በሚገኘውና የመንግሥት ይዞታ በተደረገው ደን ውስጥ በተነሣው የእሳት ቃጠሎ ሁለት ጋሻ የሚሸፍን የደኑ ይዞታ እንደ ወደመ ተገምቷል፡፡ የገዳሙ ቤተ ክርስቲያን ከሚገኝበት ቦታ በግምት ከ3 – 4 ኪ.ሜ ርቆ የተነሣውን የእሳት ቃጠሎ ለማወቅ የተቻለው ይትጎለጎል የነበረውን ጭስና የእሳቱን ነበልባል ከተመለከቱ በኋላ መሆኑን መነኰሳቱ ለዜና ሰዎች ተናግረዋል፡፡ Read the rest of this entry
%d bloggers like this: