Daily Archives: April 29, 2012

የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ?

Posted on April 29, 2012

የአሁኑን ሳምንት የኢትዮጵያ ብሎጎች ክለሳ ስሰራ ትልቁ ተግዳሮቴ የነበረው አብዛኞቹ ካሁን በፊት በዘዴ ወኪል ሰርቨርን በመጠቀም የማነባቸው  ብሎጎች አብዛኞቹ  ወኪል ሰርቨሮችም ጭምር ስለታገዱ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ድረስ ማንበብ አልቻልኩም ነበር:: ሳይደግስ አይጣላም እንዲሉ በወኪል ሰርቨሮች በኩል ማንበብ ያቃተኝን ጽሁፍ ከሀገር ውጪ ያሉ ወዳጆቼ  እንዳለ ገልብጠው በውስጥ የኢሜል አድራሻዬ  በኩል እንደ ቅጥያ ዶክመንት  ልከውልኝ ማንበብ ችያለሁ::  ሌሎች ያልታገዱ  አዳዲስ  ወኪል ሰርቨሮችንም እንድሞክራቸው ልከውልኝ መጠቀም ችያለሁ:: ስላጋጠመኝ ችግር  እና የሳምንቱ አብይ ጉዳይ ሆኖ የብዙ ብሎግ ጻሀፊያንን ትኩረት ስቦ ስለነበረው የብሎጎች እገዳ ይህችን ታህል  ካልኩ ሌሎች ምን እንዳሉ እስቲ ላቃምሳችሁ::  በፍቄን ላስቀድም በፌስቡክ ግድግዳው ላይ አጭር  ጽሁፍ አስነብቦ በብሎጉ ላይ ኢትዮጵያ መንግስት መጠላቱን የሚያሳብቁ ምልክቶች በሚል ርእስ የጻፈውን ጽሁፍ ትይይዝ አስቀምጧል:: ሙሉውን ጽሁፍ ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ይከፈቱት አልከፍት ካሎት በፍቄ  በፌስቡክ ግድግዳው ላይ ያሰቀመጠውን ጽሁፍ በማንበብ ይሞክሩት: Read the rest of this entry

የመንግሥት ሌቦች አደራ-ቢስነትና ሕዝብ ኃላፊነት

Sun, 04/29/2012

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ስለመንግሥት ሌቦች እየተናገረ ነው፤ ሌቦቹን ግን እሱም አያውቃቸው፤ እነሱም እየሰሙት አይደለም፤ የመንግስት ሌቦች የተባሉት የሚግጡባቸው ዋናዎቹ መስኮች ታክስ፣ መሬትና የንግድ ውድድር መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጾአል፤ ከዚህም በላይ የተባሉትን የሌብነት መስኮች ከለምነት ወደበረሃነት ለመለወጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ኃላፊነት አለበት ያለ መሰለኝ፤ ሥልጣን ሳይኖር ኃላፊነት ከየት ይመጣል? እንግዲህ የፌዴራል ፖሊሱንና ሌላውን አልፎ፣ የደኅንነቱን ሰራዊት አልፎ፣ የጸረ-ሙስና ኮሚሽንን አልፎ፣ ዓቃቤ ሕግን አልፎ ሕዝብ እነዚያን ለምለም መስኮች ማድረቅ እንዴት ይችላል? Read the rest of this entry

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል በሚል የወጣውን መረጃ ተከትሎ ኤርትራ ውጥረት ውስጥ ገብታለች

Sunday, April 29, 2012

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል በሚል የወጣውን መረጃ ተከትሎ ኤርትራ ውጥረት ውስጥ ገብታለች፡፡ አስመራን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች ከፍተኛ የሚሊተሪ እንቅስቃሴ መኖሩን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ላለፈው አንድ ወር ያህል ከሚዲያ የራቁት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ከዚህ ዓለም በሞት ስለመለየታቸው በእርግጠኝነት የሚናገሩ የመኖራቸውን ያህል፣ አልሞቱም ግን ኮማ ውስጥ ገብተዋል የሚሉ ወገኖችም አልጠፉም፡፡
የኤርትራ ሬዲዮና ቴሌቪዥን በበኩሉ አቶ ኢሳያስ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ‹‹ፕሬዚዳንቱ ሞተዋል›› የሚለውን የተሳሳተ መረጃ የሚያናፍሱትም ሲአይኤና ኢትዮጵያ መሆናቸውን እየገለጸ ይገኛል፡፡ በቴሌቪዥን የሚታየው የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ምስል ግን ከወራት በፊት የተቀረጸ መሆኑን ታዛቢዎች ይገልጻሉ፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ መሞታቸው በሚነገርበት በአሁኑ ጊዜ አስመራ ውስጥ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚታይ ሲሆን፣ አገሪቱን ማን ነው እየመራት ያለው የሚለው ጉዳይ ግን በግልጽ ሊታወቅ አልቻለም፡፡ Read the rest of this entry
%d bloggers like this: