Daily Archives: July 11, 2012

Supporting stability, abetting repression

By TOBIAS HAGMANN (New York Times)

BERKELEY, CALIFORNIA — Next time I travel to Ethiopia, I may be arrested as a terrorist. Why? Because I have published articles about Ethiopian politics.
I wrote a policy report on Ethiopia’s difficulties with federalism. I gave a talk in which I questioned Ethiopia’s May 2010 elections, in which the ruling EPRDF party (Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front) won 545 out of 547 seats in the Parliament. As part of my ongoing research on mass violence in the Somali territories, I interviewed members of the Ogaden National Liberation Front, a separatist rebel group in eastern Ethiopia that the government has designated as a terrorist organization.

President Barack Obama talks with Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi Read the rest of this entry

የስርአት ለውጥ መፈለግ ቅፅበታዊ ውሳኔ አይደለም!

ያለምገነት አላምረው

የወታደራዊው ስርአት ከተወገደ በሁዋላ የህዝብን ስልጣን በጠመንጃ አስፈራርቶና ዋሽቶ የወሰደው ውጥንቅጡ የጠፋበት ወያኔ መንግስት 21ኛ የጭቆናና የብዝበዛ አመቱን ወደፍፁም አምባገነንነት ተሸጋግሮ አከበረ ፡፡ የአቶ መለስ አገዛዝ የኢትዮጵያውያንን ህዝብ ትግል ውጤት( እነሱ የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው የታገለው ቢሉም) ተጠቅሞ ስልጣን ከጨበጠ ጊዜ ጀምሮ ከዕለት ዕለት ወደ ፍፁማዊ አንባገነንት በመሽጋገር ላይ ይገኛል:: Read the rest of this entry

የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በዝናብ ተጥለቀለቀ

Tags

 

 

ከፍተኛ ወጭ ተመድቦለት ግንባታውም በዚህ አመት የተጠናቀቀው እና ምርቃቱም በታላላቅ የአፍሪካ መሪዎች ባሉበት ተመርቆ በስራ ላይ የዋለው የአፍሪካ ህብረት ማእከል በትላንትናው እለት ምሽት በጣለው ከፍተኛ ዶፍ ዝናብ የህብረቱ አዳራሽ መጥለቅለቁ የደረሰን ዜና ዘገባ ያመለክታል ። ከ$200፣000 የአሜሪካን ዶላር ያወጣው እና የቀድሞውን ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዘ-ኢትዮጵያ መሰረታዊ ታሪክ ያጠፋ ከመሆኑም በላይ በመታሰቢያነት ከታሰበ ሊሰራላቸው ከሚገባቸው የሚገባው ሰዎች መካከል ቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ፣የኬንያው ጆሞ ኬኝያታ እና የግብጹ ጋማል አብዱል ናስር መሆን ሲገባቸው በምትኩ የአፍሪካ የአንድነት ታጋይ ተብለው የተሰየሙት“ በአፍሪካ አንድነት ከፍተኛ ትግል ላደረጉት በዶ/ር ክዋሚ ኑክሩማህ” ስም ሃውልት ተሰርቶ መታሰቢያ እንዲሆነላቸው የተደረገው ይሄው ሃውልት በቻይናውያን ትብብር ተሰርቶ መጠናቀቁን ባለፈው ጃንዋሪ 28 ቀን 2012 የቻይናው የፖለቲካ አድቫይሰር ጂያ ቂንጊል በተገኙበት ተመርቆ ለስራ መብቃቱ ይታወሳል :: Read the rest of this entry

ምን ያህል የዲግሪ ምሩቃን የኮብልስቶን ሰራተኞች?

“ኢትዮጲያ በበሬ ጠምዶ የሚያርስ አላጣችም መሪ እንጂ,,

 
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተምረው ዘንድሮ የሚመረቁ ተማሪዎች የመመረቂያ ልብስ (ጋውን) ለመውሰድ ሰሞኑን በግቢው ውስጥ ውር ውር ሲሉ ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ተመራቂዎች በራሳቸው ላይ ጣል የሚያደርጉት ቀልድ መረር ያለ ነው፡፡ “እንኳን ወደ ስራ ፈትነት አለም ተቀላቀልክ” “እንግሊዝኛ ተናጋሪ ኮብልስቶን ሰራተኛ” ወዘተ ዓይነት ወትሮ ያልተለመደ በራስ ላይ ቀልድ የበዛ ይመስላል – በዩኒቨርስቲው ግቢ፡፡ ለነገሩ እንዲህ ያለው ቀልድ የተጀመረው በቅርቡ ነው – በኢቴቪ፡፡ በድግሪና በዲፕሎም እንዲሁም በማስተርስ ደረጃ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከዩኒቨርስቲዎች የተመረቁ ተማሪዎች ከመንግስት ስራ ጠባቂዎች ሳይሆኑ በኮብልስቶንና በእርሻ ስራ እንደተሰማሩ የሚያሳዩ ፕሮግራሞች በቲቪ መስኮት እየቀረቡ ነው፡፡በእርግጥ አንድ ሰው በዓለም ላይ የመጨረሻውን ከፍተኛ ትምህርት ተምሮም ኮብልስቶን አነጥፋለሁ ካለ መብቱ ነው የግድ በተማርክበት ትልቅ የትምህርት ዘርፍ መስራት አለብህ ተብሎ ግዳጅ አይጣልበትም፡፡
Read the rest of this entry

ኃይሌ ገብረስላሴ ኤርትራ ኤንባሲ ምን ይሰራል!?

ኃይሌ ገብረስላሴ ኤርትራ ኤንባሲ ምን ይሰራል!?

 

ትላንት ሐምሌ 2/ 2004 ዓ.ም ታዋቂው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ኬኒያ በሚገኘው ኤርትራ ኤንባሲ መታየቱን ናይሮቢ የሚገኙ ኤርትራዊ ወዳጆቼ ነገሩኝ። ኃይሌ ገብረስላሴ ኤርትራ ኤንባሲ ምን ይሰራል!?

በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት የጭምጭምታ ወሬዎችን መናቅ አይገባም። ከዚህ በፊት ራሱ ኃይሌ ገብረስላሴን ጨምሮ ሌሎችም ራሳቸውን “ሽማግሌ” ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች ተሰባስበው በቃሊቲው እስር ቤት ሲመላለሱ ነበር። የሚል ጭምጭምታ በሰማን በማግስቱ ነው ነገሩ ሽምግልና መሆኑ የተሰማው። ማን ያውቃል አሁንም ኃይሌ ኤርትራ ኤንባሲ በታየ በነጋታው አቶ ኢሳያስ እና አቶ መለስ ሊሸማገሉ ነው የሚል ዜና እንሰማ ይሆናል። Read the rest of this entry

“እኛ የአንድም ኢትዮጵያዊ ገበሬ መሬትን አልነጠቅንም” የሰውዲ የግብርና ሚ/ር “መንግስት ከቀያችን ያፈናቀለን ሊገድልን አስቦ ነው” ተፈናቃይ አርሶ አደር

የሰውዲ አረቢያ መንግስት “ከኢትዮጵያዊያን አርሶ አደሮች ላይ ቅንጣት መሬት በሃይል አልወስደንም” ይልቁንም በአህጉሪቱ ውስጥ ላደረግነው የልማት ተሳትፎ ከመንግስት ባለስልጣናት የማበረታቻ ሙገሳዎችን አግኝተናል የላል፡፡ ተፈናቃይ አርሶ አድሮች በበኩላቸው ዛሬም ድረስ የገዢው መንግስትን ማማረራቸው ተዘገበ፡፡ በታዳጊ አገሮች በተለይ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ አየተካሄደ ነው በተባለው የመሬት መቀራመት ዘመቻ (Land Grab) በተመለከተ ከተቆርቋሪ ወገኖች ከፍተኛ ወቀሳ ከሚቀረብባቸው ባእዳን ከበረቴ አገሮች መካከል አንዱ የሆነው የሪያድ (ሰውዲ አረቢያ) መንግስት የግብርና ሚኒስትር የሆኑት ዶክተር ፋሃድ ቤን አብዱላርሃም “በልማት ስም ከመሬቱ ላይ አላግባብ የተፈናቀለ አንድም ኢትዮጵያዊ አርሶ አደር የለም፡ ወቀሳውም ቢሆን መሰረተ ቢስ ነው፡፡” Read the rest of this entry

EXCLUSIVE: Jon Voight defends Brad Pitt’s mom after she gets death threats for penning anti-Obama letter to the editor

 

 
  • angelina jolie jane pitt parents 660 reuters.JPG
     

LOS ANGELES – You can always count on family.

FOX NEWS: Last week, Brad Pitt’s mother Jane Pitt hit headlines after penning a response letter-to-the-editor of her local newspaper, Missouri’s Springfield News Leader, in which she advocated support for Republican Presidential candidate Mitt Romney, referring to him as a “a family man with high morals, business experience, who is against abortion, and shares Christian conviction concerning homosexuality.” Read the rest of this entry

ወንጀለኛው የመለስ አጃቢ (ኢየሩሳሌም አርአያ)

ከኢትዮ ሚዲያ የምርመራ ዝግጅት ክፍል ጋር በመተባበር ሕወሐት/ኢሕአዴግን የሚመለከቱ መረጃዎች በተከታታይ ይቀርባሉ። የዛሬው ጥንቅር እነሆ፦
አቶ መለስ ዜናዊ በሚደረግላቸው የተጠናከረ ልዩ የጥበቃ እንቅስቃሴ ውስጥ አዘውትሮ የማይጠፋ ሹም አለ። መለስ ከቤተ መንግስት ሲወጡም ሆነ ሲገቡ ከሚንፈላሰሱባቸው አሜሪካ ስሪት ዘመናዊ ካዲላኮች ፊት ለፊት ነጭ የፖሊስ ሞተር ሳይክል መንገዱን እየመራ ይጏዛል። ብዛት ያላቸው ሞተረኞች ከጎንና ጎን ሆነው ይከተላሉ።
መልኩ ጥቁር፣ፀጉሩ ከርዳዳ፣ጥቁር መነፅር የሚያዘወትር፣ፊቱ የማይፈታና አስፈሪ ነው። ሲናገር ቁጡና ድምፀ ጎርናና ነው። ሻምበል ታዬ ኡርጂ ይባላል። በደርግ ዘመን መቶ አለቃ የትራፊክ ፖሊስ ሞተረኞች ዋና አዛዥ፣ በመሆን በሁለቱ ስርአት ሁለቱንም መሪዎች እያገለገለ ይገኛል። Read the rest of this entry
%d bloggers like this: