Daily Archives: July 17, 2012
ሠላማዊ ትግል በአፈናና በእንግልት ሊቀለበስ አይችልም -ከአንድነት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
Share This
ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
ሐምሌ 6 ቀን 2004 ዓ/ም በሁላችንም ዘንድ ይጠበቅ የነበረው በእነ አንዱዓለም አራጌ ፋይል ክስ የተመሰረተባቸው ወንድሞቻችን ላይ ከ13 ዓመት እስከ እድሜ ልክ የሚደርስ የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ቀደም ሲል በሰጠው መግለጫ ግልፅ እንዳደረገው አብዩ ጉዳይ በፍርድ ቤት የሚሰጠው የቅጣት ውሳኔ ክብደትና ቅለት ሳይሆን ጥፋተኛ መባልና ያለመባላቸው ላይ እንደነበር ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ የሰጠው የቅጣት መጠን የሚያስተላልፈው መልዕክት ካለ የስርዓቱን ጨካኝነት እና ለስልጣኑ ስጋት ነው የሚለውን ማንኛውንም ዓይነት እንቅስቃሴ ከማፈን፤ የፍትሕ ሥርዓቱን በማንአለብኝነት በማጥቂያ መሣሪያነት ከመጠቀም ወደ ኋላ የማይል መሆኑን ነው፡፡ ኢህአዴግ ንጹሃን ዜጎችን ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ተነስተዋል እያለ ይከስሳል፡፡ የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን በማንአለብኝነት በመርገጥ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን እየናደ ያለው ግን እሱ ራሱ ነው፡፡ Read the rest of this entry
ባቢሎን በሳሎን !! ዳዊት አበበ / ኦስሎ ኖርዌይ
በኢትዮ ሜድያ ላይ አቶ ነአምን ዘለቀ የጻፉትን ወቅታዊ የትብብር ጥያቄ ጽሁፍ በአርምሞ አነበብኩት ፡፡ጽሁፉን ሳነብ ፣ ጽሑፉ ወደ አንድ ቀደም ወደ አለ ዝነኛ ጥኡም ሙዚቃ ወሰደኝ ፡፡ በዝነኛዋ ዓለም ፀሃይ ወዳጆ ተደርሶ ፣ በዝነኛው ሙሉ ቀን መለሰ ወደተዘፈነው – ምነው ከረፈደ ወደተባለው ሙዚቃ ፡፡ Read the rest of this entry
ወዳጃችን ተመስገን ደሳለኝ፤ “አቶ መለስ አዲሳባ ገብተዋል ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስቴር ግን ኃይለማርያም ደሳለኝ ሳይሆኑ አይቀሩም” ይለናል!
እንጠብቃለን!
አሁን ተሜ ይቀጥላል በፍትህ ዌብ ሳይት ላይ የወጣ ነው ይህ መረጃ እናመሰግናለን! ፍትህ ለዘላለም ትኑር!
የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ አበባ መግባት እና የፖለቲካው አሰላለፍ ህመማቸው ፀንቶ ቤልጂየም ሀገር በመታከም ላይ ይገኙ የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ትላንትና ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሕይወታቸው እንዳለፈ ሲነገር የነበረው አቶ መለስ ወደ ቤተመንግስታቸው የተመለሱት ‹‹ከህመማቸው አገግመው›› ይሁን ወይም ‹‹ከዚህ በኋላ በህክምናው አትድንም ተብለው በተስፋ መቁረጥ›› ይሁን እስከ አሁን ለማረጋገጥ አልቻልኩም። የተረጋገጠው በህይወት መግባታቸው ብቻ ነው፡፡ የአቶ መለስን መታመም ተከትሎ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ አራት ሀይሎች ‹‹በሸዋ ፖለቲካ›› ጥበብ ግብግብ ገጥመዋል። በእርግጥ አንደኛው ሀይል (ቡድን አንድ) የበላይ የመሆን ዕድሉን እያሰፋ ነው። (እኔ ካገኘሁት መረጃ አንፃር አሸናፊው ቡድን እንዲህ አይነት ገፅታ ሊኖረው ይችላል፡፡ አቀራረቤም በአገኘሁት መረጃ ላይ ተንተርሼ ለመተንተን የሞከርኩት ነው፡፡ Read the rest of this entry
Donor Dollars Aiding Political Repression In Ethiopia – OpEdBy:
Graham Peebles
An ideological poison is polluting all life within Ethiopia, flowing into every area of civil society. Local governance, urban and rural neighbourhoods, farming, education and the judiciary all are washed in Revolutionary Democracy’, Read the rest of this entry
አንቺም ጨካኝ ነበርሽ ጨካኝ አዘዘብሽ፤ እንደገና ዳቦ እሳት ነደደብሽ፡፡(ሊነበብ የሚገባው)
ይነጋል በላቸው
አንቺም ጨካኝ ነበርሽ ጨካኝ አዘዘብሽ፤ እንደገና ዳቦ እሳት ነደደብሽ፡፡ (ለአቶ መለስ ዜናዊ ፣ ከባህላዊ ሥነ ቃሎቻችን) በመሠረቱ ሞት ለሰው ልጅም ሆነ በአጠቃላይ ሕይወት ላላቸው ፍጡራን የማይቀር የመጨረሻ ዕጣ ፋንታ ነው፡፡ ማንም ከዚህ ተፈጥሯዊ ሂደት አይቀርም፡፡ ነገር ግን አሟሟት ሲያምር ለሟችም ለቋሚ ቤተሰብና ወዳጅም ደስ ይላል ብቻ ሳይሆን ያኮራል – ለዚህ ነው ሀበሻ “አሟሟቴን አሳምረው” ብሎ የሚጸልየው፡፡ ለዚህ ነው አንዳንዶች “ ከሞቴ ይልቅ አሟሟቴን እፈራለሁ” የሚሉት፡፡ አሟሟት ሲባል ደግሞ በአገባብ የተለያዩ አንድምታዎች አሉት፡፡ አሁን አዚህ የምናየው አንዱን ዘርፍ ነው፡፡ በሰው ልጆች ታሪክ እጅግ በርካታ የዓለማችን ዜጎች አጸያፊ ወይም አኩሪ ትውፊት እየተውልን በሞት ተሰናብተውን ሲያበቁ ከህልፈታቸው በኋላ በቀጣይ ትውልዶች ሲወቀሱና ሲረገሙ አሊያም ሲወደሱና ሲመረቁ ይኖራሉ፡፡ ከነዚህ በርካቶች ዜጎች መካከል ማህተመ ጋንዲንና እማሆይ ማርያ ተሬዛን በቅርብ የምናስታውሳቸው ዓለም አቀፍ ሰዎች ናቸው፡፡ በአፀደ ሕይወት ካሉት መካከልም ኔልሰን ማንዴላን መጥቀስ ይቻላል፡፡ መለስ ዜናዊ ይህችን ምድር ሊሰናበት እንደተቃረበ በስፋት እየተወራ ነው፤ የከተማችን ወሬ ከሆነም ሰነበተ፡፡ መለስ ቢሞት እርግጥ ነው አፈር አያሟሽም፡፡ ሞት በርሱ አልተጀመረምና፡፡ Read the rest of this entry
በሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የወሰደውን የሃይል እርምጃ” ተቃወሙ
በሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት የወሰደውን የሃይል እርምጃ” ተቃወሙ
ኢሳት ዜና:-በሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን “መንግስት በአዋልያና በአንዋር መስጊድ ተሰባስበው በሰላማዊ መንገድ ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄ ባቀረቡ ነዋሪዎች ላይ የወሰደውን የሃይል እርምጃ” ተቃወሙ።
ከ300 በላይ ኢትዮጵያውያን በግል ተነሳስተው በቆንስሉ ግቢ በሚገኘው የኮሚኒቲ አዳራሽ ተሰባስበው “በንጹሃን ምዕመናን ላይ የተወሰደው እርምጃ አግባብነት እንደሌለው ለማሳዎቅ፤ የታሰሩት እንዲፈቱ፤ የሞቱት ሙሉ መረጃ እንዲሰጣቸውና መንግስት የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄ ይፈታ ዘንድ አቤቱታ እንደሚያቀርቡ ” ወስነዋል፡፡፡
ተሰብሳቢዎች የመንግስት ሃላፊዎችን ለማነጋገር ጥረት ቢያደርጉም “ስብሰባው ህጋዊ ፈቃድ ሳይሰጠው የተከናዎነ ስለሆነ ማነጋገር አንችልም ” የሚል መልስ በቆንስል ሃላፊዎች መሰጠቱን ለማወቅ ተችሎአል።
Ethiopia: Dissident blogger sentenced to 18 years
Ethiopia’s federal court on Friday sentenced a prominent dissident blogger and 23 other opposition activists to long prison terms on terror charges, in a ruling that critics decried as politically motivated.
Prominent journalist and blogger Eskinder Nega, who received a prestigious press freedom award from PEN America in May, was sentenced by the court to 18 years in prison. Read the rest of this entry
Egypt journalist freed in Sudan, returns home – U
Egypt journalist freed in Sudan, returns home – U


![ETHflag_1__1_[1]](http://ethioandinet.files.wordpress.com/2012/09/ethflag_1__1_1.gif)


![60682_3922603203195_526663258_n[1] 60682_3922603203195_526663258_n[1]](http://farm9.staticflickr.com/8379/8653925962_694f997614_m.jpg)
![532059_547719218612772_154310823_n[1] 532059_547719218612772_154310823_n[1]](http://farm9.staticflickr.com/8101/8647940727_046dbca87f_m.jpg)

![524141_495401087180992_37321768_n[1] 524141_495401087180992_37321768_n[1]](http://farm9.staticflickr.com/8116/8645651087_09f9c14b6c_m.jpg)