የሻማ ማብራት በግዳጅ በየመንገዱ ይከናወናል የሰርገኞችም ከሰርጋቸው ስራት ተበተኑ

በኢትዮጵያ ውስጥ የሃዘን ቀንን አስመልክቶ በየመንገዱ የሻማ መብራት ይዘው የማይጓዙ ከሆነ በወታደሮች በግዳጅ እየተሰጠ ይገኛል። አጠቃላይ ክለቦች የተዘጉ ሲሆን በተለይም የጊዜአዊ እለታቸውን በምሯሯጥ ላይ ያሉት የቺቺንያ ሰፈር ነዋሪዎች በግዳጅ ቤቶቻቸውን እንዲዘጉ ተደርገዋል ። እኛ እቅድ ሳይኖረን በግዳጅ ሃዘን አድርጉ መባል የለብንም እኛ ስለመሞቱ እናዝናለን አዝነናልም ይህ እንደ ሰባዊ ፍጡርነቱ ልንቀበለው የምንችለው ጉዳይ ነው የምትለው ወጣቷ በአሁን ሰአት ቀድሞ ወደ ነበረን ህይወት መመለስን እንሻለን የስራተ ቀብሩን መፈጸም በጉጉት ነው የምንጠብቀው ስትል አክላ ገልጻለች

በተልይም ባሳለፍነው ሳምንት ቅዳሜ ሰርጋቸውን ሸገር መናፈሻ ያደረጉ ሙሽሮች ከሰርጋቸው በማስተጓጎል እና እድምተኞቹን በማባረር የሰርጉን ያደቅምላቸው የነበረውን ድምጻዊ ወደ ፖሊስ ጣቢያ መውሰዳቸው ከሙሽሮቹ ቤተሰቦች በተለይም ለማለዳ ታይምስ ተገልጾልናል ። በአሁኑ ጊዜ የመለስ ዜናዊን የሙት ቀን አስመልክቶ ማንኛውም ሰው እንደ ዜግነቱ ለመለስ ማዘን አለበት ተብሎ የንግድ ሱቆች ሳይቀሩ በጥቁር ልብስ ያጌጡ የንግድ ማስታወቂያ ጨርቆቻቸውን እንዲሰቅሉ ግዴታ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል ። ለረጂም ሳምንት የስራተ ቀብራቸው የተራዘመው ጠቅላይ ሚንስትሩ የቅርብ ወዳጆቻቸውን ሁሉ እያስከተሉ መጓዛቸውን ተያይዘውታል።ሀዘኑ ፈሩን እየሳተና ወደ አልሆነ አቅጣጫ እየሄደ የመጣ ይመስላል
የኢቲቪ ስህተቶች
1 የጎዳና ተዳዳሪዎች “እሱን ብለን ነው ጎዳና የወጣነው..,,,,,,
2 “እንጀራ የበላሁት በአቶ መለስ ጊዜ ነው ”
ድሮ ሳር ነበረ የምትበላው ?

3″ድሮ ቤተመንግስት አይገባም ነበረ ይሀው አሁን ለመግባት በቃሁ”
4 “የጫካው ዘንዶ ”
5 “መላው አለም ሁሉ ነው ያዘነው አለም መሪዋን ነው ያጣችው ”
6 EBS ላይ ድምፃዊት ትእግስት ወይሶ
ደህና ምግብ እንኳን በልተው የሚያውቁ አይመስለኝም ቀበቷቸው እራሱ ተፈቶ አይቻለሁ …,,,,,,እራሳቸውን አይጠብቁም ነበር….
እና የመሳሰሉት ይህ ለአቶ መለስ እና ቤተሰቦች ምን ይጠቅማቸዋል ጊዜያዊ የፓለቲካ ጨዋታ ካልሆነ በስተቀር ..,በማለት ሃዘናቸውን ገልጸዋል !
About these ads

Posted on August 27, 2012, in ETHIOPIA AMHARIC. Bookmark the permalink. Leave a Comment.

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out / Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out / Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out / Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: