የአቶ መለስ አስከሬን የት እንዳለ አይታወቅም::ስላሴ ቤተ ክርስቲያን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶ በጣም በትልቁ ተሰቅሏል: ደፍሮ የሚያነሳው ጠፍቷል!

የአቶ መለስ አስከሬን የት እንዳለ አይታወቅም::ከየት አምጥተው ሙዝየም ውስጥ እንደሚያስቀምጡት ጨንቁዋቸዋል:: አስከሬኑ ማን ጋር እንዳለ እስካሁን ማረጋገጫ አልተገኘም ::

 
 ስላሴ ቤተ ክርስቲያን “የአቡነ ጳውሎስ ፎቶ ተነስቶ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶ በግራም በቀኝም ቦታ በጣም በትልቁ ተሰቅሏል” ደፍሮ የሚያነሳው ጠፍቷል!
 
 
 
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ግብዓተ መሬት ከተፈጸመ እነሆ 5 ቀናት አለፉ ፤ አስከሬናቸው ያረፈበት ቦታ ከዚህ በፊት የማንም አስከሬን ያላረፈበት ከቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በስተ ግራ በኩል ይገኛል ፤ በቴሌቪዥን እንደተመለከታችሁት የውስጡ ግድግዳ በሴራሚክ ተነጥፎ ሳጥኑ በክብር አፈር እንዳይበላው ታስቦ አስከሬኑ አርፏል ፤ ሳጥኑ ላይ ወደፊት ሙዚየም እንደሚሰራ ታሳቢ በማድረግ ብዙ ድንጋይ እና አፈር ሊያሸክሟቻ አልወደዱም ፤ ባይሆን ትንሽ ባዞላ ቢጤ ከላይ በማስቀመጥ ክፍተቱን በሲሚንቶ በመሙላት ከላይ የኢትዮጵያ ባንዲራን አልብሰዋቸዋል ፤
 
በቀብር ስነ ስርዓት አንድ ሰው ከሞተ በኋላ የተቀበረበት ቦታ አፈር መመለስ የተለመደ ቢሆንም ይህ ነገር ግን በጠቅላይ ሚኒስትሩ አስከሬን ላይ አልተደረገም ፤ ስርዓተ ቀብሩ ከተፈጸመበት ቀን አንስቶ በርካታ ፊደራል ፖሊሶች እና የመከላከያ ሃይሎች በቦታው ይገኛሉ ፤ አስከሬናቸው ያረፈበት ቦታ ላይ 2 ሜትር በ 3 ሜትር የሆነ ቤት በአሁኑ ሰዓት ተሰርቶበታል ፤በሩ መግቢያው ላይ የኢትዮጵያ ባንዲራ ላይ ያለው ባለ 5 ኮከብ አርማ አርፎበታል ፤ ሰዎች አሁንም የተቀበሩበት ቦታ ድረስ እየሄዱ ሲያለቅሱ ተስተውለዋል ፤ ያረፉበትንም ቦታ ለማየት እስከአሁን ድረስ በርከት ያሉ ሰዎች ወደ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሲመጡ ተስተውሏል ፤ ቦታው ላይ ምን ለመስራት እንዳሰቡ ባናውቅም መሰረተ ልማት ለመገንባት የሚያስችል ሸክላዎች ፤ ሲሚንቶዎች ፤ በርካታ ትላልቅ ብረቶች ፤ እንጨቶችና የተለያዩ መሳሪያዎች በቦታው ላይ እየተራገፈ ይገኛል ፤ አስከሬናቸው ሙዝየም ውስጥ ከተቀመጠ ለምን ይህን ሁሉ ነገር ይደረጋል? ሲሉ ሰዎች ሲያወሩ ይደመጣሉ ፤ ባሳለፍናቸው 4 ቀናት ውስጥ ይህ ነው የሚባል ለውጥ ባይኖርም አሁን ግን አስከሬኑ ያረፈበትን በአማካይ 300 ካሬ የሚሆን ቦታ በላስቲክ የማጠር ስራ እየተሰራ ይገኛል ፤ ሀውልቱን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ነው እንዳይባል አስከሬናቸው ሌላ ቦታ ያርፋል ተብሏል ፤ ታዲያ ለምን ይህን ያህል ቦታ ማጠር አስፈለገ ? 4 ካሬ የማይበልጥ ቦታ ላይ ያረፈን አስከሬን ስራ ለመስራት ይህ ያህል ቦታ ማጠር አስፈላጊነቱ አልታየንም ፤ ወደፊት ይህ ቦታ የታጠረው ላስቲክ ተነስቶ ለቤተክርስትያኒቱ ምዕመናን የቀድሞውን ቅዳሴ የማስቀደሻ ፤ በዓል ማክበሪያ እና መሰል አገልግሎቶችን ይሰጣል ብለን አሁን መናገር አንችልም::

የአቡነ ጳውሎስ ፎቶ ያለበት ሸራ የቀብራቸው እለት በቤተክርስትያኑ በስተግራ በኩል መሰቀሉ ይታወሳል ፤ ከሁለት ቀን በኋላ ግን የአቡነ ጳውሎስ ፎቶ ተነስቶ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶ በግራም በቀኝም ቦታ በጣም በትልቁ ተሰቅሏል ፤ መጀመሪያ እኛ የአቡነ ጳውሎስን ፎቶ ሰቅለን ባናሳያቸው ኖሮ እነርሱም ፎቷውን ለመስቀል ጥያቄ ባላቀረቡ ነበር ፤ መሰቀሉን ለምን? እያልን ሳይሆን የተሰቀለበት ቦታ ግን አግባብ ነው የሚል ሀሳብ የለንም ፤ ፎቶው ዛሬ ከተሰቀለ 7 ቀን ሞልቶታል እስከመቼ እንደሚቆይ አይታወቅም ፤ የጥላሁን ገሰሰ ፎቶ የሞተ ሰሞን በእጁ ማይኩን ይዞ በትልቁ በግቢው ውስጥ መሰቀሉ የዛሬ 3 ዓመት ትውስታችን ነው ፤ የጥላሁንን ፎቶ ማይክ ይዞ በግቢው ውስጥ የተመለከቱ ጥቂት ሰዎች በሁኔታው ደስተኛ አለመሆናቸው በጊዜው ሲገልጡ ነበር ፤ ለምን ? ብለው ቢጠይቁም መልስ የሚመልስ ሰው አይገኝም ፤ ቤተክርስትያን ውስጥ በትልቁ እንዲህ አይነት ፎቶ መመልከት ለአማኙ ምን አይነት መንፈስ ውስጥ እንደሚያስገባው ማወቅ አይከብድም ፤ በጊዜው ጥቂት ወጣቶች “ኮንሰርት ያለበት ነው የሚመስው” እያሉም ሲቀልዱ ተስተውሏል ፤ ስለዚህ የቤተክርስትያንን ግቢ እኛው መደረግ ያለበትንና የሌለበትን ለይተን ማወቅ መቻል አለብን ፡፡
 
5ኪሎ ቅድስት ማርያም በሩ ላይ ቆመው ሲሳለሙ ከፊት ለፊት ያለው የአቡነ ጳውሎስ ፎቶ ይመለከታሉ ፤ አሁን ደግሞ ቅድስት ሥላሴ ሄደው እጅዎትን ወደላይ አንስተው ለማማተብ ሲሉ ከፊት የሚታይዎት ሌላ ነገር ነው ፤እነዚህ ነገሮች ከጊዜ ወዲህ የመጡ ተለጣፊ ነገሮችን እየለመድናቸው መጥተን ወደፊት ሌላ ነገር እንዳይፈጥሩ ፍራቻ አለን ፤ ከዓመታት በፊት የአቡነ ጳውሎስ በየቤተክርስትያኑ የተሰቀሉት ፎቶዎች ቅዱስ ሲኖዶስ ይነሱ ብሎ መወሰኑ የሚታወቅ ነው ፤ ማንሳት ሲያቅተን ለአእምሯችን ተገቢ ነው ብለን ነግረነው ካበቃን በኋላ አሁን ብናያቸውም ባናያቸውም ምንም ላይመስለን ይችላል ፤ ነገር ግን አግባብ አለመሆኑን ግን ማወቅ አለብን ፤ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ፎቶም ቢሰቀል አግባብ የሚሆነው አስከሬናቸው ያረፈበት ቦታ ቢሆን መልካም ነው ፤ እንደ አሁኑ ተደርጎ መሰቀሉ ግን አግባብ ነው አንልም(ከተሳሳትን እንታረማለን)፡፡
ቸር ሰንብቱ
About these ads

Posted on September 8, 2012, in ETHIOPIA AMHARIC. Bookmark the permalink. Leave a Comment.

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out / Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out / Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out / Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: