በቀጣይነት ግንቦት ሰባት እና ተባባሪዎቹ የሚወስዱት እርምጃ ስጋት የሆነበት ወያኔ የሚያሰለጥናቸውን የደህንነት አባላቱን በሃገር ውስጥ በሚገኙ የተመዘገቡ የተቃዋሚ ድርጅቶች መዋቅር ውስጥ እና በኢሕአዴግ የወረዳ መዋቅሮች ውስጥ በማቀናጀት እንደሚመድባቸው እና እንዲሁም በጎረቤት አገራት በድንበር ከተሞች እና በዋና ዋና ከተሞች እንደሚመደቡ የህብረተሰቡን እንቅስቃሴ እና የግንኙነት መረብ በማጥናት መረጃ በመሰብሰብ ሪፖርት እንደሚያደርጉ ታውቋል።
ከዚህ ቀደም በዚህ የደህንነት መዋቅር ስራ ላይ የተመደቡ የወያኔ አባላት ይህን ያህል የሚያረካ ውጤት እና መረጃ ካለማምጣታቸውም በላይ አሁን ከሚመደቡ ጋር በጋራ እንዲሰሩ እንደሚደረግ ታውቋል።